ሙሉ ዓለም ባህል ማዕከል የተውኔት ድርሰቶችን መዝኖ በቁርጥ ክፍያ ለመግዛት ይፈልጋል
የተውኔት ግዥ ማስታዎቂያ
ሙሉ ዓለም ባህል ማዕከል ከዚህ በታች በተዘረዘሩየ ተውኔት ድርሰቶችን መዝኖ በቁርጥ ክፍያ ለመግዛት ይፈልጋል፣
የሚቀርቡ የፈጠራ ሥራዎች አይነት
1. የሙሉ ጊዜ የመድረክ ተውኔት
- በኮምፒውተር ሲፃፍ ከ55 ገፅ ያላነሰ፣
- በመድረክ ሲቀርብ ከ2 ሰዓት እስከ 2፡30 የጊዜ ቆይታ የሚሸፍን፣
- ግለወጥ የሆነ /ከሌላ ያልተኮረጀ/፣
2. ባለ አንድ ገቢር የመድረክ ተውኔት
- በኮምፒውተር ሲፃፍ ከ25 እስከ 35 ገጽ ብዛት ያለው
- በመድረክ ሲቀርብ ከ45 ደቂቃ እስከ 1፡00 የጊዜ ቆይታ የሚሸፍን
- ገፀ-ባህሪያቱ የተመጠኑ
- ግለወጥ /ከሌላ ያልተኮረጀ/
3. የሕፃናት ተውኔት ድርሰት
- በኮምፒውተር ሲፃፍ ከ15-20 ገፅ የሚደርስ
- በመድረክ ሲቀርብ ከ30-40 ደቂቃ የሚሸፍን
- ጭብጡ የህፃናትን አእምሮ ያገናዘበ
- ገፀ-ባህሪያቱ የተመጠኑ
- ግለወጥ ወይም ተዛማጅ ትርጉም
ተውኔቶች ተገምግመው በ3ቱም ዘርፎች የተመረጡ ድርሰቶች በማዕከሉ የግዥ ፎርማሊቲ መሰረት ግዥ ይፈፀማል፡፡ ተወዳዳሪዎች ሥራቸውን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥቅምት 27 ድረስ ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ለማዕከሉ የት/ት/ጥ/ጥ/ምር/ ስል/ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 3 ማቅረብ ይችላሉ፡፡
ለበለጠ መረጃ 09 18 00 98 94 ወይም 09 18 70 85 18 በመደወል ማረጋገጥ ይችላሉ፡፡
ማሳሰቢያ፡- ተወዳዳሪዎች ሙሉ ስማቸውን፣ የስልክ ወይም የፖስታ ቁጥራቸውን እና የመኖሪያ አድራሻቸውን በግልጽ ከቨር ገፅ ላይ ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል፡፡
የሙሉ ዓለም የባህል ማዕከል
No comments:
Post a Comment